ለስፖርት አበረታች ቅመሞች ምርመራና ቁጥጥር ባለሙያዎች ስልጠና እየተሰጠ ነው ፡፡
ግንቦት 20/2013 ዓ/ም
የኢትዮጵያ ብሔራዊ የፀረ-አበረታች ቅመሞች ጽ/ቤት /ETH-NADO/ አዘጋጅነት የስፖርት አበረታች ቅመሞች ወይም ዶፒንግ ምርመራና ቁጥጥር ባለሙያዎች በዶፒንግ ምርመራና ቁጥጥር እና አጠቃላይ እንቅስቃሴ ዙሪያ በአዳማ ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል ፡፡
በመድረኩ 55 የሚሆኑ የዶፒንግ ምርመራና ቁጥጥር የበጎ ፍቃድ ባለሙያዎች /Chaperones , DCOs and BCOs / ተሳትፈዋል ።
ለሁለት ቀናት በሚቆየው ስልጠና በ2021 የተከለሰው የምርመራ ባለሙያዎች መመሪያ ሰነድ ፣ የምርመራ ባለሙያዎች የደረጃ እድገትና የስራ ስምሪት ፣ በምርመራና ቁጥጥር ስራዎች ላይ የነበሩ ጠንካራና ደካማ ጎኖች ዙሪያ እንዲሁም የጽ/ቤቱ የ10 ወር የስራ አፈጻጸም በባለሙያዎች ቀርበው ውይይት፣ የሚደረግባቸው ይሆናል ።
May be an image of 1 person and indoor
May be an image of one or more people, people standing, people sitting and indoor
May be an image of one or more people, people sitting, people standing and indoor
May be an image of 2 people, people standing, people sitting and indoor
May be an image of 1 person, standing and indoor

By Ermias

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *