ባለፉት ጊዜያት በአገራችን ኢትዮጵያ የስፖር አበረታች ቅመሞችን ወይም ዶፒንግን ለመከላከልና ለመቆጣጠር ተቋማዊ አደረጃጀቱን ማጠናከርን ጨምሮ የተካሄደው እንቅስቃሴ ውጤታማ በሆነ መልኩ መፈፀሙን የአለም አቀፉ የፀረ-ዶፒንግ ኤጀንሲ (WADA) አስታወቀ።

በአለም አቀፍ ህጎችና ስታንዳርዶች መሰረት በየደረጃው ጠንካራና ቀጣይነት ያለው የፀረ-ዶፒንግ ስርዓት ለመዘርጋት የኢትዮጵያ ብሄራዊ የፀረ-አበረታች ቅመሞች ፅ/ቤት ከአለም አቀፉ የፀረ-ዶፒንግ ኤጀንሲ (WADA) እና ከደቡብ አፍሪካ የፀረ-ዶፒንግ ተቋም ጋር የሶስትዮሽ የፓርትነርሽፕ ፕሮግራም በመቅረፅ ተግባራዊ ሲደረግ የቆየ ሲሆን የሚፈለገውን ስኬት ማስመዝገብ መቻሉን አፈፃፀሙ በተገመገመበት ወቅት ተጠቁሟል።

ይህ ውጤት በአፍሪካ ደረጃም ንፁህ ስፖርት ለማስፋፋት ከፍተኛ እንደሚኖረው ኤጀንሲው በድረ-ገፁ ላይ ባወጣው መግለጫ አመላክቷል።

ዝርዝር መረጃውን በሚቀጥለው Link ላይ ማግኘት ይችላሉ።

 

https://www.wada-ama.org/en/media/news/2020-05/wada-hails-south-africa-ethiopia-nado-partnership-a-success-for-clean-sport-in?fbclid=IwAR3NRUDTcmUbI-UQ09aO7K0ryuN45tfBpITLpXVHrA9tztPxUxR0fBOmS40

 ይመልከቱ