በስፖርቱ ውስጥ በየደረጃው ለሚያገለግሉ ባለሞያዎች በስፖርት አበረታች ቅመሞች ወይም ዶፒንግ ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ፡፡
Read Time:36 Second
ታህሳስ 17/2011 ዓ.ም
በአገራችን በርካታ ባለሞያዎች በተለያዩ የስፖርት አይነቶች ሰልጥነው በአሰልጣኝነት፣ በዳኝነት፣ በኢንስትራክተርነት እና በመሳሰሉት ዘርፎች በማገልገል ላይ እንደሚገኙ ይታወቃል፡፡ ስለሆነም እነዚህ የስፖርት ባለሞያዎች በአገር አቀፍ ደረጃ አበረታች ቅመሞችን ወይም ዶፒንግን በመከላከልና በመቆጣጠር ንፁህ ስፖርትን በማስፋፋት ረገድ ሰፊ ሚና እንደሚጫወቱ ይታመናል፡፡
በመሆኑን የኢትዮጵያ ብሄራዊ የፀረ-አበረታች ቅመሞች ፅ/ቤት ከፌዴራል ስፖርት ኮሚሽን ጋር በመተባበር ዩኒቨርሲቲዎችን ጨምሮ ከሁሉም ክልሎች/የከተማ አስተዳደሮች ለተወጣጡ እና ከላይ እንደተገለፀው በ19 የስፖርት አይነቶች በአሰልጣኝነት፣ በዳኝነት እና በኢንስትራክተርነት ለሚያገለግሉ 610 የስፖርት ባለሞያዎች በአበረታች ቅመሞች ወይም ዶፒንግ መሰረታዊ ጉዳዮች፣ በየደረጃው በተዘረጉ የአሰራር ስርዓቶችና አደረጃጀቶች፤ በህግ ማዕቀፎች እና በተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያ በአዳማ ከተማ ስልጠና ተሰጥቷል፡፡
ይህ ስልጠና በቀጣይም ተጠንክሮ የሚቀጥል ሲሆን በየደረጃው የሚገኙ ባለድርሻ አካላትን ተደራሽ ለማድረግ እና ሰፊ የህዝብ ንቅናቄ ለመፍጠር ፅ/ቤቱ ትኩረት ሰጥቶ የሚሰራ ይሆናል፡፡
Related Post
በሀዋሳ ክለብ ውስጥ ለሚገኙ የተለያዩ ስፖርተኞች፣ አሰልጣኞች እና አመራሮች ሰልጠና ተሰጥቷል ፡፡
በስፖርት አበረታች ቅመሞች ወይም ዶፒንግ ዙሪያ በሀዋሳ ክለብ ውስጥ ለሚገኙ የተለያዩ ስፖርተኞች፣ አሰልጣኞች እና አመራሮች ሰልጠና ተሰጥቷል ፡፡ ቀን ፡-...
# ከዶፒንግ የጸዳ ስፖርት እና ስፖርተኞችን እናፈራለን !!!
# ከዶፒንግ የጸዳ ስፖርት እና ስፖርተኞችን እናፈራለን !!! በሐዋሳ ከተማ በመካሄድ ላይ ያለው ለስፖርት ማሰልጠኛ ተቋማት ስፖርተኞች አሰልጣኞች እና የስፖርት...
ሀገረሰላማ አትሌቲክስ ማሰልጠኛ ማዕከል
በአዲሲቷ የሲዳማ ብሔራዊ ክልል ውስጥ በሚገኘው ሀገረሰላማ አትሌቲክስ ማሰልጠኛ ማዕከል ውስጥ ለሚገኙ አትሌቶች እና አሰልጣኞች በዶፒንግ ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና...
ለሐዋሳ ዩንቨርስቲ የ2013 ዓ/ም የመጀመሪያ ድግሪ የስፖርት ሳይንስ ተመራቂ ተማሪዎች
ለሐዋሳ ዩንቨርስቲ የ2013 ዓ/ም የመጀመሪያ ድግሪ የስፖርት ሳይንስ ተመራቂ ተማሪዎች እና መምህራን በአበረታች ቅመሞች ወይም ዶፒንግ ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና...
ከደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ክልል እና ከሲዳማ ክልል ለተወጣጡ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ የፀረ-አበረታች ቅመሞች ጽ/ቤት/ETH-NADO/ ከደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ክልል እና ከሲዳማ ክልል ለተወጣጡ ለህክምና ፤ የስነ-ምግብ እና ወጌሻ ባለሞያዎች...
አበረታች ቅመሞችን (ዶፒንግን) በመከላከል ረገድ የህክምና ባለሙያዎች ሚና ከፍተኛ ነው ተባለ፡፡
አበረታች ቅመሞችን (ዶፒንግን) በመከላከል ረገድ የህክምና ባለሙያዎች ሚና ከፍተኛ ነው ተባለ፡፡ ቀን፡- መጋቢት 13/ 2013 ዓ.ም ሐዋሳ ሴንትራል ሆቴል በሐዋሳ...
Average Rating