ለሐዋሳ ዩንቨርስቲ የ2013 ዓ/ም የመጀመሪያ ድግሪ የስፖርት ሳይንስ ተመራቂ ተማሪዎች
Read Time:40 Second
ለሐዋሳ ዩንቨርስቲ የ2013 ዓ/ም የመጀመሪያ ድግሪ የስፖርት ሳይንስ ተመራቂ ተማሪዎች እና መምህራን በአበረታች ቅመሞች ወይም ዶፒንግ ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ።
ቀን ፡- መጋቢት 14/2013
ቦታ ፡- ሐዋሳ ዩኒቨርስቲ
የኢትዮጲያ ብሔራዊ ጸረ- አበረታች ቅመሞች ጽ/ቤት ምክትል ዳሬክተር ወ/ሮ ፋንታዩ ገዛኸኝ የስልጠና ፕሮግራሙን በከፈቱበት ወቅት ባደረጉት ንግግር ጽ/ቤቱ የነበሩበን ፈታኝ ሁኔታዎችን በማለፍ አሁን ላይ ግንዛቤ መፍጠርና ማሳደግ ላይ በስፋት እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል ፡፡
የስፖርት ሳይንስ ተማሪዎች ከስፖርቱ ጋር ያላችሁ ቁርኝት ከፍተኛ በመሆኑ በስፖርት በአበረታች ቅመሞች ዙሪያ የግንዛቤ እንዲኖራችሁ ማድረጉ ጤናማ የሆኑ ተተኪ አትሌቶቸን ለማፍራት አስተዋጾ አለው ብለዋል ። አያይዘውም በዶፒንግ ዙሪያ ያላቸውን ግንዛቤ ጽ/ቤቱ በሚያሰራጨቸው የተለያዩ መረጃዎችን በመጠቀም ማጎልበት እንደሚገባ ተናግረዋል ፡፡
ስለጠናውን 90 የሚበልጡ የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች እና መምህራን ተከታትለውታል ፡፡
ስልጠናው በትምህርት እና ስልጠና ባለሙያዎች የቀረበ ሲሆን በዶፒንግ ምንነት፣ ህግ ጥሰት፣የአትሌቶች መብትና ግዴታ፣፣ የዶፒንግ የምርመራ ሂደት እና በተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ ያተኮረ ነው፡፡





Related Post
በሀዋሳ ክለብ ውስጥ ለሚገኙ የተለያዩ ስፖርተኞች፣ አሰልጣኞች እና አመራሮች ሰልጠና ተሰጥቷል ፡፡
በስፖርት አበረታች ቅመሞች ወይም ዶፒንግ ዙሪያ በሀዋሳ ክለብ ውስጥ ለሚገኙ የተለያዩ ስፖርተኞች፣ አሰልጣኞች እና አመራሮች ሰልጠና ተሰጥቷል ፡፡ ቀን ፡-...
# ከዶፒንግ የጸዳ ስፖርት እና ስፖርተኞችን እናፈራለን !!!
# ከዶፒንግ የጸዳ ስፖርት እና ስፖርተኞችን እናፈራለን !!! በሐዋሳ ከተማ በመካሄድ ላይ ያለው ለስፖርት ማሰልጠኛ ተቋማት ስፖርተኞች አሰልጣኞች እና የስፖርት...
ሀገረሰላማ አትሌቲክስ ማሰልጠኛ ማዕከል
በአዲሲቷ የሲዳማ ብሔራዊ ክልል ውስጥ በሚገኘው ሀገረሰላማ አትሌቲክስ ማሰልጠኛ ማዕከል ውስጥ ለሚገኙ አትሌቶች እና አሰልጣኞች በዶፒንግ ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና...
ከደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ክልል እና ከሲዳማ ክልል ለተወጣጡ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ የፀረ-አበረታች ቅመሞች ጽ/ቤት/ETH-NADO/ ከደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ክልል እና ከሲዳማ ክልል ለተወጣጡ ለህክምና ፤ የስነ-ምግብ እና ወጌሻ ባለሞያዎች...
አበረታች ቅመሞችን (ዶፒንግን) በመከላከል ረገድ የህክምና ባለሙያዎች ሚና ከፍተኛ ነው ተባለ፡፡
አበረታች ቅመሞችን (ዶፒንግን) በመከላከል ረገድ የህክምና ባለሙያዎች ሚና ከፍተኛ ነው ተባለ፡፡ ቀን፡- መጋቢት 13/ 2013 ዓ.ም ሐዋሳ ሴንትራል ሆቴል በሐዋሳ...
ለኢትዮጵያ ብሔራዊ አትሌቲክስ ቡድን በዶፒንግ ፅንሰ-ሃሳብ ስልጠና ተሰጠ::
ቀን፡- ሀሙስ መጋቢት 9/2013 ዓ.ም ቦታ ፡- ጥሩነሽ ዲባባ ሆቴል ለገጣፎ እና አሰለፈች ሆቴል አዲስ አበባ የኢትዮጵያ ብሔራዊ የፀረ-አበረታች ቅመሞች...
Average Rating