በጽ /ቤቱ የአስር አመት መሪ ዕቅድ ላይ ውይይት ተካሄደ፡፡
ቀን፡29/1/2013ዓ.ም
ቦታ፡- አዳማ ጀርመን ሆቴል
በዛሬው የሁለተኛ ቀን የውይይት ፕሮግራም የኢትዮጵያ ብሔራዊ የፀረ-አበረታች ቅመሞች ፅ/ቤት ማናጅመት አባላትና ሰራተኞች የአስር አመት መሪ ዕቅድ ላይ ውይይት አካሄዱ፡፡
የኢትዮጵያ ብሔራዊ የፀረ-አበረታች ቅመሞች ጽ/ቤት ም/ ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ፋንታዪ ገዛኽኝ ውይይቱን በመሩበት ወቅት እዳመለከቱት የውይይቱ ዓላማ የጽ/ቤቱ አመራርና ሰራተኞች የአስር አመቱን መሪ ዕቅድ ላይ ግባት ለማሰባሰብና የጋራ ግንዛቤ እዲጨብጡ ለማስቻል እደሆነ አመልክተዋል፡፡
የእቅድና በጀት ደይሬክቶሬ ዳይሬክተር የሆኑት አቶ አብዲሳ የጽ/ቤቱን የቀጣይ በአስር አመት ስትራቴጂክ ዕቅድ(20123-2020) ላይ ገለጻ አድርገዋል፡፡
ጽ/ቤቱ በአገር አቀፍ ደረጃ ዶፒንግን ለመከላከልና ለቆጣጣር እየተካሄደ ያለውን እንቅስቃሴ ለማጎልበት በአበረታች ቅመሞችን ወይም ዶፒንግ ዙሪያ የላቀ ሚና መጫወት እደሚጠበቅበት ም/ ዋና ዳይሬክተሯ በዚህ ወቅት አሳስበዋል፡፡
በቀጣይ በኣስር አመቱ መሪ እቅድ ዙሪያ ከባለድረሻ አካላትና ከሚመለከታቸው ጋር ውይይት እንደ ሚካሄድና ግዕባት እደሚሰባስብ ገልጸዋል፡፡
በተመሳሳይ በባላስድ ስኮርካርድ ዙሪያ በጽ/ቤቱ የሰው ኃብት ፤ግዥና ንብረት አሰተዳደር ዳ/ዳይሬክተር በአቶ ፍቅሩ ንጉሴ ገለጻ ተድረጓል ፡፡
በነገው ዕለት የ3ኛ ቀን ፕሮግራም በ2013 በጀት አመት አቅድ ላይ ውይይት ይካሄየዳል፡፡
![](https://scontent.fjib1-2.fna.fbcdn.net/v/t1.0-0/s600x600/121172262_680401519522280_1659307104722712519_o.jpg?_nc_cat=109&_nc_sid=8bfeb9&_nc_ohc=0SPHRA9OE4kAX8L8YEf&_nc_ht=scontent.fjib1-2.fna&tp=7&oh=60c18ba060617561d3511a15383e642d&oe=5FAA1441)
![](https://scontent.fjib1-2.fna.fbcdn.net/v/t1.0-0/s600x600/121230927_680401552855610_3693992765424214074_o.jpg?_nc_cat=110&_nc_sid=8bfeb9&_nc_ohc=vOXWqO_diYkAX-7f5PD&_nc_ht=scontent.fjib1-2.fna&tp=7&oh=61b852ac6f26ac15944b04f9bfa83b1f&oe=5FAB0E9B)
![](https://scontent.fjib1-1.fna.fbcdn.net/v/t1.0-0/s600x600/121222916_680401559522276_1336192283836277697_o.jpg?_nc_cat=103&_nc_sid=8bfeb9&_nc_ohc=q7TSDz_CNdkAX8szqHf&_nc_ht=scontent.fjib1-1.fna&tp=7&oh=445c42d4919aa6a318a542d91b0c96f9&oe=5FAA36BF)
![](https://scontent.fjib1-2.fna.fbcdn.net/v/t1.0-9/121195905_680401529522279_4883040158990687540_o.jpg?_nc_cat=110&_nc_sid=8bfeb9&_nc_ohc=7twbbBhHp4IAX9VpI14&_nc_oc=AQmmlwkYUKhJPxIXcl37SuPehY0AZdc7DF5sjJROmvANfGwEpgVfhHDBNUKnl1mAmME&_nc_ht=scontent.fjib1-2.fna&oh=433cb96d7023be5a511dbc03ab818ebe&oe=5FAB105F)