ጽ/ቤታችን /ETH-NADO/ በኮቪድ-19 ምክንያት ለችግር ለተጋለጡ ወገኖች ድጋፍ አደረገ
ቀን-ቅዳሜ ግንቦት 15 ቀን 2012 ዓ.ም
ቦታ፡-አዲስ አበባ ስቴዲየም
  የኢትዮጵያ ብሔራዊ ፀረ-አበረታች ቅመሞች ጽ/ቤት በስታድዪም ዙሪያ ለሚገኙ የጎዳና ተዳዳሪዎች ለ2ኛው ዙር የምገባ ፕሮግራም ድጋፍ የሚውል የ2 መቶ ሺ ብር ስጦታ አበረከተ፡፡
   የኢፌድሪ ስፖርት ኮሚሽን ከተባባሪ አካላት ጋር የምገባ ፕሮግራሙን ግንቦት 15 ቀን 2012 ዓ.ም በአዲስ አበባ ስቴዲዮም ይፋ በዳረግበት ወቅት ላይ የተገኙት የጽ/ቤታችን ምክትል ዋና ዳሬክተር ወ/ሮ ፋንታዬ ገዛህኝ እደገለጹት ለወገወን ደራሽ ወገን በመሆኑ በኮረና ቫይረስ ለችግር የተጋለጡ ወገኖቻችን ለመታደግ ጽ/ቤታችን ድጋፍ በማድረጉ ደሰታ ይሰማዋል ብለዋል፡፡
                               
   ወ/ሮ ፋንታዬ አክለውም ጽ/ቤታችን የምገባ ፕሮግራሙን ሲደግፍ የተጣለበትን ማሀበራዊ ኃላፊነት ለመወጣት ካለው ብርቱ ፍላጎት አንጻርም እደሆን አበራርትተዋል፡፡
   በተለይ በአትሌት ኮማንደር ደራቱ ቱሉና በአትሌት አልማዝ አያና የተደረገው እገዛ መልካምና አኩሪ ተግባር ነው፡፡ለሌሎች የስፖርቱ ቤተሰብ አራዓያ አደሆን ተናግረዋል፡፡
   ም/ዋና ዳይሬከተር አያይዘው እደገለጹት በኮረና ወረርሽን ምክንያት ተቋርጦ የነበረው የአትሌቶች የዶፒነግ ምርመራና ቁጥጥር እንደሚጀመር አስታውቀው፤አትሌቶች የኮረና ቫይረስ የጥንቃቄ እርምጃዎችን በመከተል፤እራሳቸውን ከዶፒንግ እዲያርቁ አሳስበዋል፡፡
ፕሮግራሙን በይፋ ያስጀመሩት የኢፌድሪ ሰፖርት ኮሚሽን ከሚሺነር አቶ ኢሊያስ ሽኩርና ሌሎች ከፍተኛ መንግስት ባለሰልጣናት ናቸው፡፡
የምገባ ፕሮግራሙ የጠቅላይ ሚኒሰተር ክብር ዶ/ር አብይ አህመድ መዕድ መጋራት እኒሼቲፍ አካል ነው፡፡

By Ermias

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *