ጽ/ቤቱ /ETH-NADO/ የ10 ዓመት ስትራቴጂክ ዕቅድ ፤ የ2012 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም እና በ2013 ዕቅድ ላይ ውይይት ጀመረ፡፡
የ2012 በጀት አመት ዕቅድ አፈጻጸም መልካም እደነበር ተገለጸ፤
,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,
ቀን፤ሀሙስ መስከረም 28/1/2013 ዓ.ም
ቦታ፤ አዳማ ጀርመን ሆቴል
የኢትዮጵያ ብሔራዊ የፀረ-አበረታች ቅመሞች ጽ/ቤት የ10 ዓመት መሪ ዕቅድ፤የ2012 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም እና በ2013 ዕቅድ ላይ ከጽ/ቤቱ አመራሮችና ሰራተኞች ጋር መወያየት ጀመረ፡፡
ውይይቱ ከመስከረም28-30/2013 ዓ.ም ድረስ የሚቆይ ሲሆን፡፡ በዛሬው ዕለት የ2012 በጀት አመት እቅ ድ ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል ፡፡የኢትዮጵያ ብሔራዊ የፀረ-አበረታች ቅመሞች ጽ/ቤት ዋና ዳይሬክተር አቶ መኮንን ይደርሳል በቀረበው ሪፖርት ዙርያ ሰፊ ማብራሪያ ሰተዋል፡፡በበጀት አመቱ የተቋሙን እቅድ ከማዘጋጀት፤የትምህርትና ስልጠና፤ የህዝብ ንቅናቄ እዲሁም በየደረጃው የምርመራና ቁጥጥር በኩል ሰፊ ስራዎች መከናዎናቸው የተገለጸ ሲሆን ፤ ሚዲያና ኮሚኒኬሽን፤ የቁጥጥርና የክትትል በየርከኑ ተጠናክረው እዲቀጥል በማድረግ በኩል ስራዎች በእቅድ መሰርት እተከናወኑ መቆየታቸውን ፤አለም ዓቀፍ ግኑኝ ነት የማጎልበት ስራዎች ውጤታማ በሆነ መልኩ መከናወናችውን ዋና ዳይሬክተሩ ገልጸዋል፡፡
ጽ/ቤቱ የነበረው አፈጻጸም መልካም የሚባል ሲሆን ነገር ግን በግምገማ መድረኩ ላይ የተጠቀሱ ክፍተቶችን በመድፈን በኩል ሰፊ ስራ መስራት አደሚገባው ተገልጻል ፡፡
በመጨረሻ ከመድረኩ ለተነሳው ጥያቄ የጽ/ቤቱ አመራሮች ዋና ዳይሬክተሩ አቶ መኮንን ይደርሳልና ም/ ዋና ዳይሬክተሯ ወ/ሮ ፋንታዪ ገዛህኝ ምላሽ ተሰጥቶበታል፡፡
ውይይቱ በነገው እለት የሚቀጥል ሲሆን የ10 አመቱ የስትራቴጂ እቅድ ቀርቦ ውይይት ይደረግበታል ፡፡
![](https://scontent.fjib1-1.fna.fbcdn.net/v/t1.0-0/s600x600/121111068_679881152907650_2398252233756532214_o.jpg?_nc_cat=108&_nc_sid=8bfeb9&_nc_ohc=4Hb7kbFPrH4AX-gF0RF&_nc_ht=scontent.fjib1-1.fna&tp=7&oh=0c8734536c54a154f6d558b3bdc1520c&oe=5FAB7613)
![](https://scontent.fjib1-2.fna.fbcdn.net/v/t1.0-0/s600x600/121216786_679881282907637_1017331685495412643_o.jpg?_nc_cat=107&_nc_sid=8bfeb9&_nc_ohc=0vLDi3P8tB0AX8XQDiV&_nc_ht=scontent.fjib1-2.fna&tp=7&oh=54ecb4b858a5aa90b54b36ebc6859b49&oe=5FAB05EF)