በ39ኛው ጃን-ሜዳ ሃገርአቋራጭ ውድድር ላይ የፀረ-ዶፒንግ የቅስቀሳና Outreaching ፕሮግራሙ ተካሄደ

Williams Brown

Lorem ipsum dolor sit amet, consectetur adipisicing elit. Dolor, alias aspernatur quam voluptates sint, dolore doloribus voluptas labore temporibus earum eveniet, reiciendis.

Tags


በ39ኛው ጃን-ሜዳ ሃገርአቋራጭ ውድድር ላይ የፀረ-ዶፒንግ የቅስቀሳና Outreaching ፕሮግራሙ ተካሄደ
የኢትዮጵያ የፀረ-አበረታች ቅመሞች ባለሥልጣን (ETH-ADA) ለ39ኛ ግዜ የካቲት 06/2014 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ በተከሄደው የጃን – ሜዳ እና የምስራቅ አፈሪካ ኢንተርናሽናል ሃገር አቋራጭ ውድድር ላይ ለተሳተፉ የስፖርተኞችና የስፖርት ባለሞያዎች እንዲሁም የስፖርቱን ማህበረሰብ ግንዛቤ ለማሳደግ እና ሰፊ ንቅናቄ ለመፍጠር የፀረ-ዶፒንግ የOutreaching ፕሮግራም አካሂደዋል፡;
በዚህ ውድድር ላይ የተለያዩ የቅስቀሳና ፕሮሞሽን ማቴሪያሎች ፤ ብሮሸሮች ፣ የፊት ማስክዎች፤ ለስፖርተኞች ፣ ለስፖርት ባለሞያዎች፣ለስፖርት አመራሮችና ሌሎችንም ተሳታፊዎች የተሰራጨ ሲሆን በተለይ አሳታፊ የሆኑ፤አትሌቶችን በቀላሉ ግንዛቤ እዲጨብጡየሚያስችል የጥያቄና መልስ ውድድር ተካሂዷል በተጨማሪ የተለያዩ መልዕክት የሚያስተላልፉ ባነሮች ተዘጋጅተው ለዕይታ በሚያመች ቦታዎች እዲሰቀሉተደርጓል::
በውድድሩ ከምስራቅ አፍሪካ ሃገራት፤ከክልል፤ ከተማ አስተዳደሮች፤ ከክለቦች፤ ከዩኒቨረሲቲዎች፤ ከአትሌቲክስ ማሰልጠኛ ማዕከላት፤ ከተቋማትና የግል ተወዳዳሪዎች የተውጣቱ በርካታ አዋቂ እና ወጣት አትሌቶች ተሳትፈዋል፡፡