የኢፌድሪ ስፖርት ኮሚሸን ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ፀረ አበረታች ቅመሞች ፅ/ቤት እና ከኢትዮጵያ ስፖርት ጋዜጠኞች ማህበር ጋር በመተባባር ለስፖርት ጋዜጠኞች ባያዘጋጀው የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ተጠናቋል ::
በአዳማ ከተማ ለሁለት ቀናት ሲካሄድ የቆየው የጋዜጠኞች የውይይት መድረክ ሲጠናቀቅ በስፖርት ዘገባ ልምድና በጋዜጠኞች ሙያዊ ስነ-ምግባር ዙሪያ የተዘጋጀ ጽሑፍ በክቡር ዶክተር ጌታቸው ድንቁ የኢትዮጲያ ብሮድካስቲንግ ባለስልጣን ዋና ዳሬክተር ቀርቧል::
የስፖርት ጋዜጠኝነት አጀማመር ፤ የመገናኛ ብዙሃን እና የሚዲያ ባለሙያዎች በማህበረሰቡ ዘንድ ሊኖራቸው የሚገቡ ድርሻ ምን መሆን አለበት ፤ በዘገባ ወቅት ሊኖሩ የሚገቡ የቋንቋ አጠቃቀም ፤ የመገናኛ ብዙሃን ዝርዝር ዓላማዎች ፤ የመገናኛ ብዙሃን ሊኖሯቸው የሚገቡ አመቺ ሁኔታዎች እና ያሉባቸውን አስቸጋሪ ሁኔታዎች በሚሉ ጉዳዮች ዙሪያ በዝርዝር ግንዛቤ መፍጠር በሚያስችል መልኩ ስልጠና ተሠጥቷል ::
በመጨረሻም የቀረበው ጽሑፍ መነሻ በማደረግ የጋራ ውይይት ተደረጎባቸው የእለቱ ፕሮግራም ተጠናቋል ።
![](https://scontent.fadd1-1.fna.fbcdn.net/v/t1.0-0/p600x600/149818846_768500094045755_149584207655301037_n.jpg?_nc_cat=102&ccb=3&_nc_sid=8bfeb9&_nc_ohc=kVF3vzkin80AX-w4SqN&_nc_ht=scontent.fadd1-1.fna&tp=6&oh=fbffdfacc9056bcc64addab977d9d15a&oe=604F157E)
![](https://scontent.fadd1-1.fna.fbcdn.net/v/t1.0-0/p600x600/149448720_768500254045739_5277030700935512062_n.jpg?_nc_cat=100&ccb=3&_nc_sid=8bfeb9&_nc_ohc=o19EZB0nFt8AX-8lDF_&_nc_ht=scontent.fadd1-1.fna&tp=6&oh=18a277f756eb13e9c4ab3fdc6774a0a3&oe=604F883A)
![](https://scontent.fadd1-1.fna.fbcdn.net/v/t1.0-0/p600x600/150028766_768500390712392_6097581153393190827_n.jpg?_nc_cat=100&ccb=3&_nc_sid=8bfeb9&_nc_ohc=L2wFMvuL4jkAX8OF9ZF&_nc_ht=scontent.fadd1-1.fna&tp=6&oh=2237d0c2dbea32ff562aae463fa92e86&oe=60507ACB)
![](https://scontent.fadd1-1.fna.fbcdn.net/v/t1.0-0/p600x600/149652161_768500454045719_3689868380369517621_n.jpg?_nc_cat=102&ccb=3&_nc_sid=8bfeb9&_nc_ohc=X7SUN5BD-U0AX9gN1LH&_nc_ht=scontent.fadd1-1.fna&tp=6&oh=3e536165e766365024e243f4c8dbf8f7&oe=604E0765)