ጽ/ቤቱ /ETH-NADO/ የ10 ዓመት ስትራቴጂክ ዕቅድ ፤ የ2012 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም እና በ2013 ዕቅድ ላይ ውይይት ጀመረ፡፡ የ2012 በጀት አመት ዕቅድ አፈጻጸም መልካም እደነበር ተገለጸ፤

Williams Brown

Lorem ipsum dolor sit amet, consectetur adipisicing elit. Dolor, alias aspernatur quam voluptates sint, dolore doloribus voluptas labore temporibus earum eveniet, reiciendis.

Tags


ጽ/ቤቱ /ETH-NADO/ የ10 ዓመት ስትራቴጂክ ዕቅድ ፤ የ2012 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም እና በ2013 ዕቅድ ላይ ውይይት ጀመረ፡፡
የ2012 በጀት አመት ዕቅድ አፈጻጸም መልካም እደነበር ተገለጸ፤
,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,
ቀን፤ሀሙስ መስከረም 28/1/2013 ዓ.ም
ቦታ፤ አዳማ ጀርመን ሆቴል
የኢትዮጵያ ብሔራዊ የፀረ-አበረታች ቅመሞች ጽ/ቤት የ10 ዓመት መሪ ዕቅድ፤የ2012 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም እና በ2013 ዕቅድ ላይ ከጽ/ቤቱ አመራሮችና ሰራተኞች ጋር መወያየት ጀመረ፡፡
ውይይቱ ከመስከረም28-30/2013 ዓ.ም ድረስ የሚቆይ ሲሆን፡፡ በዛሬው ዕለት የ2012 በጀት አመት እቅ ድ ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል ፡፡የኢትዮጵያ ብሔራዊ የፀረ-አበረታች ቅመሞች ጽ/ቤት ዋና ዳይሬክተር አቶ መኮንን ይደርሳል በቀረበው ሪፖርት ዙርያ ሰፊ ማብራሪያ ሰተዋል፡፡በበጀት አመቱ የተቋሙን እቅድ ከማዘጋጀት፤የትምህርትና ስልጠና፤ የህዝብ ንቅናቄ እዲሁም በየደረጃው የምርመራና ቁጥጥር በኩል ሰፊ ስራዎች መከናዎናቸው የተገለጸ ሲሆን ፤ ሚዲያና ኮሚኒኬሽን፤ የቁጥጥርና የክትትል በየርከኑ ተጠናክረው እዲቀጥል በማድረግ በኩል ስራዎች በእቅድ መሰርት እተከናወኑ መቆየታቸውን ፤አለም ዓቀፍ ግኑኝ ነት የማጎልበት ስራዎች ውጤታማ በሆነ መልኩ መከናወናችውን ዋና ዳይሬክተሩ ገልጸዋል፡፡
ጽ/ቤቱ የነበረው አፈጻጸም መልካም የሚባል ሲሆን ነገር ግን በግምገማ መድረኩ ላይ የተጠቀሱ ክፍተቶችን በመድፈን በኩል ሰፊ ስራ መስራት አደሚገባው ተገልጻል ፡፡
በመጨረሻ ከመድረኩ ለተነሳው ጥያቄ የጽ/ቤቱ አመራሮች ዋና ዳይሬክተሩ አቶ መኮንን ይደርሳልና ም/ ዋና ዳይሬክተሯ ወ/ሮ ፋንታዪ ገዛህኝ ምላሽ ተሰጥቶበታል፡፡
ውይይቱ በነገው እለት የሚቀጥል ሲሆን የ10 አመቱ የስትራቴጂ እቅድ ቀርቦ ውይይት ይደረግበታል ፡፡